በ2030 ዓ.ም የንፁህ መጠጥ ውሃን ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ፡፡
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር “በተግዳሮቶች ፊት መፅናት” በሚል መሪ ሃሳብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ተደራሽነት ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ የባለ ብዙ ባለድርሻ ምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።
በዚሁ ወቅት ሚኒስትሩ እንዳመለከቱት፤ በ2030 ዓ.ም የንፁህ መጠጥ ውሃ በገጠርና በከተማ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል።
ይህንን ዕቅድ እውን ለማድረግም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የንፁህ ውሃ አቅርቦትን ማሳደግ ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ባለው በዚህ የባለ ብዙ ባለድርሻ መድረክ የፌደራልና ክልሎች መንግስታት፣ የልማት አጋሮች፣ የሲቪል ማህበራትና የሙያ ማህበራት ተገኝተዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።