በ2030 ዓ.ም የንፁህ መጠጥ ውሃን ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ፡፡
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር “በተግዳሮቶች ፊት መፅናት” በሚል መሪ ሃሳብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ተደራሽነት ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ የባለ ብዙ ባለድርሻ ምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።
በዚሁ ወቅት ሚኒስትሩ እንዳመለከቱት፤ በ2030 ዓ.ም የንፁህ መጠጥ ውሃ በገጠርና በከተማ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል።
ይህንን ዕቅድ እውን ለማድረግም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የንፁህ ውሃ አቅርቦትን ማሳደግ ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ባለው በዚህ የባለ ብዙ ባለድርሻ መድረክ የፌደራልና ክልሎች መንግስታት፣ የልማት አጋሮች፣ የሲቪል ማህበራትና የሙያ ማህበራት ተገኝተዋል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።