በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አብዱልሃኪም ሙሉ በአርሲ ዞን የተገነቡ ፕሮጀክቶችን እየመረቁ ነው፡፡
ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጥራት ደረጃ እና ጊዜ ተገንብተው መመረቃቸውንም አቶ አብዱልሃኪም ገልጸዋል፡፡
ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የኢተያ ገጠር ሽግግር ማዕከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው÷ ማዕከሉ በአካባቢው ያለውን የግብርና ግብዓት እሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል፡፡
የኦሮሚያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ መንግሥቱ ረጋሳ በበኩላቸው በክልሉ ተመሳሳይ ሥድስት ማዕከላት መገንባታቸውን በመግለጽ÷ የማዕከላቱ መገንባት ለአርሶ አደሮችም ሆነ ለባለሃብቶች ከፍተኛ ጥቅም አለው ብለዋል፡፡
ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 1 ሺህ 61 ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ ፕሮጀክቶች በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት መሠራታቸውን የገለጹት ደግሞ አርሲ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ኢብራሂም ከድር ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በዞኑ እየተመረቁ ለሚገኙ ፕሮጀክቶችም 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ወጪ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።