በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አብዱልሃኪም ሙሉ በአርሲ ዞን የተገነቡ ፕሮጀክቶችን እየመረቁ ነው፡፡
ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጥራት ደረጃ እና ጊዜ ተገንብተው መመረቃቸውንም አቶ አብዱልሃኪም ገልጸዋል፡፡
ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የኢተያ ገጠር ሽግግር ማዕከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው÷ ማዕከሉ በአካባቢው ያለውን የግብርና ግብዓት እሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል፡፡
የኦሮሚያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ መንግሥቱ ረጋሳ በበኩላቸው በክልሉ ተመሳሳይ ሥድስት ማዕከላት መገንባታቸውን በመግለጽ÷ የማዕከላቱ መገንባት ለአርሶ አደሮችም ሆነ ለባለሃብቶች ከፍተኛ ጥቅም አለው ብለዋል፡፡
ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 1 ሺህ 61 ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ ፕሮጀክቶች በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት መሠራታቸውን የገለጹት ደግሞ አርሲ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ኢብራሂም ከድር ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በዞኑ እየተመረቁ ለሚገኙ ፕሮጀክቶችም 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ወጪ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
በጥናት ምርምር የተደገፍ ማህበረሰብ ተኮር ተግባራትን ከመፈፀም ባሻገር በጥሩ ስነ ምግባርና እወቀት የታነፁ ትውልድን ከመቅረፅ አኳያ የዩንቨርስቲ መምህራኖች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለጹ።
በዘንድሮ ዓመት በሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አጠቃላይ ከሚፈተኑ 19ሺህ በላይ ተማሪዎች ዉስጥ ከ2ሺህ 6መቶ በላይ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተና እንደሚፈተኑ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።