በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አብዱልሃኪም ሙሉ በአርሲ ዞን የተገነቡ ፕሮጀክቶችን እየመረቁ ነው፡፡
ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጥራት ደረጃ እና ጊዜ ተገንብተው መመረቃቸውንም አቶ አብዱልሃኪም ገልጸዋል፡፡
ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የኢተያ ገጠር ሽግግር ማዕከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው÷ ማዕከሉ በአካባቢው ያለውን የግብርና ግብዓት እሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል፡፡
የኦሮሚያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ መንግሥቱ ረጋሳ በበኩላቸው በክልሉ ተመሳሳይ ሥድስት ማዕከላት መገንባታቸውን በመግለጽ÷ የማዕከላቱ መገንባት ለአርሶ አደሮችም ሆነ ለባለሃብቶች ከፍተኛ ጥቅም አለው ብለዋል፡፡
ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 1 ሺህ 61 ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ ፕሮጀክቶች በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት መሠራታቸውን የገለጹት ደግሞ አርሲ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ኢብራሂም ከድር ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በዞኑ እየተመረቁ ለሚገኙ ፕሮጀክቶችም 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ወጪ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።