ወጣቶች በሀገራዊ ምክክሩ ሚናቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያዘጋጀው የወጣቶች የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መሥፍን አርአያ (ፕ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ ወቅት ÷ ወጣቶች የመነጋገርና የመደማመጥ ባህልን በማጎልበት በሀገራዊ ምክክሩ ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል ፡፡
ለሰላምና ለተረጋጋ የሀገረ መንግስት ግንባታ የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በመድረኩ በትውልዶች መካከል መኖር ስለሚገባው ምክክር እንዲሁም በሀገራዊ ምክክሩ የወጣቶችን ሚና ማሳደግ ስለሚቻልባቸው መንገዶች የውይይት መነሻ ሃሳብ ቀርቧል።
እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ከ200 በላይ ወጣቶች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።