ወጣቶች በሀገራዊ ምክክሩ ሚናቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ያዘጋጀው የወጣቶች የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መሥፍን አርአያ (ፕ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ ወቅት ÷ ወጣቶች የመነጋገርና የመደማመጥ ባህልን በማጎልበት በሀገራዊ ምክክሩ ሚናቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል ፡፡
ለሰላምና ለተረጋጋ የሀገረ መንግስት ግንባታ የወጣቶች ሚና ከፍተኛ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በመድረኩ በትውልዶች መካከል መኖር ስለሚገባው ምክክር እንዲሁም በሀገራዊ ምክክሩ የወጣቶችን ሚና ማሳደግ ስለሚቻልባቸው መንገዶች የውይይት መነሻ ሃሳብ ቀርቧል።
እየተካሄደ በሚገኘው ውይይት ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ከ200 በላይ ወጣቶች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን ከኮሚሽኑ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።