ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ኢትዮጵያና ዑጋንዳ በቀጣናው ሰላምና ፀጥታን በማስፈን ረገድ ጉልህ ሚና አላቸው አሉOn Jul 3, 2024 73አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ዑጋንዳ ካላቸው ጠንካራ ስትራቴጂክ ግንኙነት በተጨማሪ በቀጣናው ሰላምና ፀጥታን በማስፈን ረገድ ጉልህ ሚና እንዳላቸው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አስገነዘቡ፡፡ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ከዑጋንዳ ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር ተወያይተዋል፡፡በውይይታቸውም ኢትዮጵያ እና ዑጋንዳ ካላቸው ጠንካራ ስትራቴጂክ ግንኙነት በተጨማሪ በቀጣናው ሰላምና ፀጥታን በማስፈን ረገድ ጉልህ ሚና እንዳላቸው ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ አስረድተዋል፡፡ሁለቱ ሀገራት በመከላከያ ዘርፍ የሚያደርጉት ትብብርም ፋይዳው የጎላ ስለመሆኑ ማስገንዘባቸውን የመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ መረጃ አመላክቷል፡፡ፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ በበኩላቸው ዑጋንዳና ኢትዮጵያ ዘመናትን የተሻገረ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ወዳጅነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አውስተዋል፡፡ሀገራቱ በመከላከያ ዘርፍ እንዲሁም በቀጣናው ሰላም በማስፈን ረገድ ያላቸውን የጋራ ሚናና ትብብር በማስቀጠል ቀጣናው ብሎም አፍሪካ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ እንደሚገባቸውም አመላክተዋል፡፡
FBC
More Stories
በጥናት ምርምር የተደገፍ ማህበረሰብ ተኮር ተግባራትን ከመፈፀም ባሻገር በጥሩ ስነ ምግባርና እወቀት የታነፁ ትውልድን ከመቅረፅ አኳያ የዩንቨርስቲ መምህራኖች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለጹ።
በዘንድሮ ዓመት በሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አጠቃላይ ከሚፈተኑ 19ሺህ በላይ ተማሪዎች ዉስጥ ከ2ሺህ 6መቶ በላይ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተና እንደሚፈተኑ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።