የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአዲስ አበባ የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) የተመራ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ አባላት ገለፃ በማድረግ አስጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ከፒያሳ አራት ኪሎ እና ከሜክሲኮ ሣር ቤት የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ ተደርጎባቸዋል። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ፕሮጀክቱ የአፍሪካ መዲና የሆነችውን አዲስ አበባ እንደስሟ አዲስና ልዩ ከተማ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።
EBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ