የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአዲስ አበባ የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ጉብኝቱ በምክር ቤቱ የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) የተመራ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለምክር ቤቱ አባላት ገለፃ በማድረግ አስጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ከፒያሳ አራት ኪሎ እና ከሜክሲኮ ሣር ቤት የተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ምልከታ ተደርጎባቸዋል። የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፤ ፕሮጀክቱ የአፍሪካ መዲና የሆነችውን አዲስ አበባ እንደስሟ አዲስና ልዩ ከተማ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል።
EBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …