የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ስዊስ ዲያግኖስቲክስ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል፡፡ የህክምና ማዕከሉ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን ራዕይ ለማሳካት እንደሚያግዝ ከንቲባዋ ገልጸዋል፡፡ የማዕከሉ አገልግሎት እንዲስፋፋ እና ሌሎች የግል ባለሃብቶች በጤናው ዘርፍ ይበልጥ እንዲሰማሩ የከተማ አስተዳደሩ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል፡፡ መሰል የጤና ማዕከላት መበራከት ከሃገር ወጥተው መታከም የማይችሉ ወገኖች የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ ከማስቻሉም ባሻገር የውጪ ምንዛሬን እንደሚያስቀር ከንቲባዋ በማኀበራዊ የትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።