ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የቆየ ወታደራዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት የውጭ ጉዳይና መከላከያ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ሴናተር ስቴፋኒያ ክራክሲ ገለጹ።
የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) እና ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በጣሊያን ምክር ቤት በሴናተር ስቴፋኒያ ክራክሲ የተመራ የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡
በዚሁ ወቅትም ሴናተሯ ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የቆየ ወታደራዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ፍላጎት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሀገራት ወሳኝ ሚና ያላት መሆኗን አንስተው፤ ሀገራቸው በሁለንተናዊ መልኩ ከኢትዮጵያ ጋር አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትፈልግ መግለጻቸውን የመከላከያ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትን ዋቢ አድርጎ የመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ አመልክቷል።
አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) በበኩላቸው በኢትዮጵያና በጣሊያን መካካል ያለውን የቆየ ወታደራዊ ትብብር ከፍ ወዳለና ወደላቀ ደረጃ ለማሳደግ ጣሊያን ላሳየችው ፍላጎት አመስግነዋል።
ኢትዮጵያ ከጣሊያን ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከር ከፍተኛ ፍላጎት ያላት መሆኗንም አረጋግጠዋል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።