ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የቆየ ወታደራዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት የውጭ ጉዳይና መከላከያ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ሴናተር ስቴፋኒያ ክራክሲ ገለጹ።
የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ (ኢ/ር) እና ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በጣሊያን ምክር ቤት በሴናተር ስቴፋኒያ ክራክሲ የተመራ የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡
በዚሁ ወቅትም ሴናተሯ ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የቆየ ወታደራዊ ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ፍላጎት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሀገራት ወሳኝ ሚና ያላት መሆኗን አንስተው፤ ሀገራቸው በሁለንተናዊ መልኩ ከኢትዮጵያ ጋር አጋርነቷን ማጠናከር እንደምትፈልግ መግለጻቸውን የመከላከያ ሚኒስትር ጽህፈት ቤትን ዋቢ አድርጎ የመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ አመልክቷል።
አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) በበኩላቸው በኢትዮጵያና በጣሊያን መካካል ያለውን የቆየ ወታደራዊ ትብብር ከፍ ወዳለና ወደላቀ ደረጃ ለማሳደግ ጣሊያን ላሳየችው ፍላጎት አመስግነዋል።
ኢትዮጵያ ከጣሊያን ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከር ከፍተኛ ፍላጎት ያላት መሆኗንም አረጋግጠዋል።
FBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …