የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ከኬንያ መንገድ እና ትራንስፖርት ካቢኔ ፀሃፊ ኪፕቹምባ ሞርኮሜን ጋር በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ በናይሮቢ ተወያይተዋል።በውይይታቸውም የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ጉዳዮች ላይ የተወያዩ ሲሆን፤ በተለይም ሁለቱን ሀገራት በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል የጋራ የንግድ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ማድረጋቸው ተገልጿል።በውይይቱ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ መሳተፋቸውን ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።