የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኢንዱስትሪው የአቪዬሽን ኦስካር ተብሎ በሚጠራው የስካይትራክስ መድረክ ለ7ኛ ጊዜ የአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ ሽልማትን አሸንፏል፡፡አየር መንገዱ በተጨማሪም የአፍሪካ ምርጥ የቢዝነስ ክፍል አየር መንገድ ሽልማትን ለ6 ተከታታይ ዓመታት ማሸነፉ ተገልጿል፡፡እንዲሁም አየር መንገዱ የአፍሪካ ምርጥ የኢኮኖሚ ክፍል አየር መንገድ ሽልማትን ለ6 ተከታታይ ዓመት ማሸነፍ ነው የተጠቆመው፡፡ከዚህ ባለፈም በአፍሪካ የኢኮኖሚ ክፍል ምርጥ ምግብ አገልግሎት ሰጪ አየር መንገድ ሽልማትን ማሸነፉን የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል፡፡ውጤቱን ተከትሎም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በስኬቶቹ ሁሉ አብረውት ለተጓዙ ደንበኞች ምስጋና አቅርቧል፡፡
FBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ