የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኢንዱስትሪው የአቪዬሽን ኦስካር ተብሎ በሚጠራው የስካይትራክስ መድረክ ለ7ኛ ጊዜ የአፍሪካ ምርጡ አየር መንገድ ሽልማትን አሸንፏል፡፡አየር መንገዱ በተጨማሪም የአፍሪካ ምርጥ የቢዝነስ ክፍል አየር መንገድ ሽልማትን ለ6 ተከታታይ ዓመታት ማሸነፉ ተገልጿል፡፡እንዲሁም አየር መንገዱ የአፍሪካ ምርጥ የኢኮኖሚ ክፍል አየር መንገድ ሽልማትን ለ6 ተከታታይ ዓመት ማሸነፍ ነው የተጠቆመው፡፡ከዚህ ባለፈም በአፍሪካ የኢኮኖሚ ክፍል ምርጥ ምግብ አገልግሎት ሰጪ አየር መንገድ ሽልማትን ማሸነፉን የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል፡፡ውጤቱን ተከትሎም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በስኬቶቹ ሁሉ አብረውት ለተጓዙ ደንበኞች ምስጋና አቅርቧል፡፡
FBC
More Stories
እንግሊዝን ያስቆጣው የኢራን ጥቃት
በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በሌማት ትሩፋት መርሐግብር የተሠማሩ ወጣቶች ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣቸው ተገለጸ።
ኢራን ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ወታደራዊ ዘመቻ …