አጠር ያሉ ጉዞዎች በመኪና፣ በአውቶቡስ እና በባቡር መደረጋቸው የተለመደ ነው።ዌስትሬይ እና ፓፓ ዌስትሬይ በሚባሉት የስኮትላንድ ደሴቶች መካከል የሚደረገው የአውሮፕላን ጉዞ የዓለማችን አጭሩ በረራ በመሆን ተመዝግቧል።በደሴቶቹ መካከል ያለው ርቀት 2.7 ኪሎ ሜትር ሲሆን፤ ነዋሪዎች ከአንዱ ደሴት ወደ ሌላው ለማምራት ሁለት አማራጮች እንዳሏቸው ተገልጿል።በጀልባ መጓዝ አንዱ አማራጭ ሲሆን፤ ሌላኛው እና በነዋሪዎቹ ተመራጭ የሆነው አነስ ባለ አውሮፕላን የአየር ጉዞ ማድረግ ነው።የአየር ላይ ጉዞው 2 ደቂቃን እንደሚፈጅ የተገለፀ ሲሆን፤ ጥሩ የአየር ሁኔታ ካለ ከዚያም ሊያንስ እንደሚችል ነው የተገለፀው።ከ17 እስከ 45 ዩሮ የሚያስከፍለው ይህ ጉዞ በክረምት ወቅት ብዙ ቱሪስቶችን እንደሚስተናግድም ተገልጿል።
የዓለማችን አጭሩ በረራ
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።