የኢፌዴሪ መከላከያ ጀኔራል መኮንኖች አዲስ አበባ ከሚኖሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ጋር በዛሬው ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የአማራ ክልል የሰላም ኮንፈረንሰ ውይይት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተደርጓል፡፡
ወይይቱን የመሩት የክልሉ ተወላጅ የሆኑት የጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ ÷ የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ እንዲሁም የመከላከያ ዘመቻ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል በላይ ስዩም ናቸው።
ተሳታፊዎችም አለ የሚሉትን ችግር በነፃነት በጥያቄም በሃሳብም የገለፁ ሲሆን ÷ ጥያቄያቸው ለክልል መንግስት እና ለፌደራል መንግስት ተደራጅቶ እንደሚቀርብ ተገልጿል።
በጉባኤው ማጠቃለያው የመድረኩ ተሳታፊዎች ባለ 7 ነጥብ የአቋም መግለጫም አውጥተዋል መባሉን የመከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።