ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት ምክንያት ከጥቅምት 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተዘግቶ መቆየቱ ይታወቃል።ጽ/ቤቱ ሰኔ 11፣ 2016 ዓ.ም ዳግም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን፤ በጊዜያዊነት የጀመራቸው አገልግሎቶች ፓስፖርት ማደስ፣ የጠፋ ፓስፖርት መተካት እና የተበላሸ ፓስፖርት እርማት መስጠት ናቸው።በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ፓስፖርታቸውን ሲያሳድሱ የነበሩ የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች የቅርንጫፉ አገልግሎት በመቋረጡ ምክንያት አዲስ አበባ ድረስ ለመሄድ ይገደዱ እንደነበር ገልጸዋል።በዚህም ለአላስፈላጊ እንግልት ተዳርገው እንደነበር ጠቅሰው ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዳግም ስራ በመጀመሩ መደሰታቸውን መግለጻቸውን ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።