በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የመገናኛ ብዙኃን ሚናን የተመለከተ መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሕዝብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አረጋዊ በርሄን (ዶ/ር) ጨምሮ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
በውይይቱም የመገናኛ ብዙኃን ባለፉት ዓመታት ፕሮጀክቱ አሁን ላለበት ቁመና እንዲደር ስ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ማድረጋቸውን አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
ግድቡ እስከሚጠናቀቅ እንዲሁም የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መሰረተ-ልማቶች እስከሚዘረጉ ድረስ መገናኛ ብዙኃን ቀሪ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል፡፡
ተቋማቱ ከዚህ ቀደም ካከናወኗቸው ሥራዎች ባለፈ የዓባይን ታሪክ፣ የግንባታ ሂደቱንና ለኢትዮጵያ ያለውን አስተዋፅዖ ለቀጣዩ ትውልድ ሠንዶ ማስተላለፍ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል፡፡
ይህም ቀጣዩ ትውልድ ዓባይን በልኩ እንዲረዳ፣ ከተረጅነት ተላቆ ነፃ ኢኮኖሚን መገንባት እንዲችል ብሎም በዲፕሎማሲው መስክ በንቃት እንዲሳተፍ ያግዛል ነው ያሉት፡፡
በአጠቃላይ ግድቡ ከሚኖሩት 13 ተርባይኖች አሁን ላይ ሁለቱ ኃይል እያመነጩ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።