በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የመገናኛ ብዙኃን ሚናን የተመለከተ መድረክ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሕዝብ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አረጋዊ በርሄን (ዶ/ር) ጨምሮ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
በውይይቱም የመገናኛ ብዙኃን ባለፉት ዓመታት ፕሮጀክቱ አሁን ላለበት ቁመና እንዲደር ስ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ማድረጋቸውን አረጋዊ በርሄ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
ግድቡ እስከሚጠናቀቅ እንዲሁም የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መሰረተ-ልማቶች እስከሚዘረጉ ድረስ መገናኛ ብዙኃን ቀሪ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል፡፡
ተቋማቱ ከዚህ ቀደም ካከናወኗቸው ሥራዎች ባለፈ የዓባይን ታሪክ፣ የግንባታ ሂደቱንና ለኢትዮጵያ ያለውን አስተዋፅዖ ለቀጣዩ ትውልድ ሠንዶ ማስተላለፍ እንደሚጠበቅባቸውም አስገንዝበዋል፡፡
ይህም ቀጣዩ ትውልድ ዓባይን በልኩ እንዲረዳ፣ ከተረጅነት ተላቆ ነፃ ኢኮኖሚን መገንባት እንዲችል ብሎም በዲፕሎማሲው መስክ በንቃት እንዲሳተፍ ያግዛል ነው ያሉት፡፡
በአጠቃላይ ግድቡ ከሚኖሩት 13 ተርባይኖች አሁን ላይ ሁለቱ ኃይል እያመነጩ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
FBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ