1445ኛው የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል የኢድ ሶላት በደመቀና ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ መጠናቀቁን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ሃይል አስታውቋል፡፡የኢድ ሶላት በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በታደሙበት እጅግ በደመቀና በዓሉን በሚመጥን ሃይማኖታዊ ሥርዓት መጠናቀቁን ነው የጋራ ግብረ-ሃይሉ የገለጸው፡፡በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስቀድሞ የተደረገውን ዝግጅት የሚመጥን የተግባር አፈፃፀም ላሳዩ መላው የፀጥታ አካላትን አመስግኗል፡፡እንዲሁም ለበዓሉ ሠላማዊነት ለፀጥታ ሐይሉ ሥራ ተባባሪ በመሆን የድርሻቸውን ለተወጡ የዕምነቱ ተከታዬችና ለሰላም ወዳዱ የከተማው ነዋሪ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል ምስጋና አቅርቧል፡፡የጋራ ግብረ-ሃይሉ ለመላው የዕምነቱ ተከታዮች በዓሉ የፍቅር፣ የሠላም፣ የጤና እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።
FBC
More Stories
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ታላቁን የክብር ኒሻን ለቢል ጌትስ ሸለሙ
በ9 ነጥብ 3 ሚለየን ብር የተገዛው የሞተር ሳይክልና የታብሌት ሞባይል ለዞኖች ድጋፍ ተደረገ
የኢትዮጵያን መፃዒ ዕድል የተሻለ ለማድረግ ሀገራዊ ምክክሩ የማይተካ ሚና አለው-የፌደራል ተቋማትና ማህበራት ተሳታፊዎች