1445ኛው የኢድል አል አድሃ (አረፋ) በዓል የኢድ ሶላት በደመቀና ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ መጠናቀቁን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ሃይል አስታውቋል፡፡የኢድ ሶላት በርካታ የዕምነቱ ተከታዮች በታደሙበት እጅግ በደመቀና በዓሉን በሚመጥን ሃይማኖታዊ ሥርዓት መጠናቀቁን ነው የጋራ ግብረ-ሃይሉ የገለጸው፡፡በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስቀድሞ የተደረገውን ዝግጅት የሚመጥን የተግባር አፈፃፀም ላሳዩ መላው የፀጥታ አካላትን አመስግኗል፡፡እንዲሁም ለበዓሉ ሠላማዊነት ለፀጥታ ሐይሉ ሥራ ተባባሪ በመሆን የድርሻቸውን ለተወጡ የዕምነቱ ተከታዬችና ለሰላም ወዳዱ የከተማው ነዋሪ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል ምስጋና አቅርቧል፡፡የጋራ ግብረ-ሃይሉ ለመላው የዕምነቱ ተከታዮች በዓሉ የፍቅር፣ የሠላም፣ የጤና እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።