የበጀት ዓመቱ የመጨረሻ የ100 ቀናት አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ÷ ባለፉት 10 ወራት ንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትና ሳኒቴሽን ዘርፍ የተኛለ ስራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡በዚህም አሁን ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ72 ሚሊየን ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡“ግድቤን በደጄ” በሚል ፕሮጀክትም በድርቅ የሚጎዱ አካባቢዎች የዝናብ ውሃን በማሰባሰብ ተጠቃሚ የሚሆኑበት ስራ በስፋት መከናወኑንም ጠቁመዋል፡፡ይህም በቀጣይ በሌሎች አከባቢዎች እንሰዲሰፋ ይሰራል ነው ያሉት፡፡ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ በተለያዩ ተቋማት ሲመሩ የነበሩ የመጠጥ ውሃ ቁፋሮና መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቶችን በተቀናጀ አግባብ መምራት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት በፍጥነት አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡በዚህም ከውሃና ኢነርጂ ዘርፍ በተጨማሪ ከግብርና እንዲሁም ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት በመስራት ያለውን ሃብት በውጤታማነት መጠቀም መቻሉን ገልጸዋል።ለአብነት በተንዳሆ ግድብ ላይ በቅንጅት በተሰራው ህብረተሰቡን የመስኖ ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር በውጤታማነት ጎርፍ የመከላከል ሥራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡በዚህም መንግስት ያወጣው የነበረውን ተጨማሪ ወጪ ማስቀረት ተችሏል ነው ያሉት፡፡በቀጣይም ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ለኢዜአ ተናግረዋል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።