የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የችግሩ አሳሳቢነት ግን እየከፋ መሆኑን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
የመንገድ ደህንነትን ማስጠበቅ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።
በምክክር መድረኩ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ÷በኢትዮጵያ የትራፊክ አደጋ የሰው ህይወትን በመቅጠፍ፣አካል በማጉደል እና ንብረትን በማውደም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን ተናግረዋል።
የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የችግሩ አሳሳቢነት ግን እየከፋ መሆኑን ገልፀዋል።
በመሆኑም ይህን ችግር ለመከላከል በቅንጅት በመስራት መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በውይይቱ የክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች የመንገድ ደህንነት ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ሲሆን÷ የትራፊክ አደጋን መከላከል ያልተቻለባቸውን ምክንያቶች በመለየት መሠራት ያለባቸው የመፍትሄ ሀሳቦች እንደሚቀመጡ ተገልጿል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።