የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከናይጄሪያ ፌዴራል ሪፐብሊክ የጦር ኮሌጅ ጋር “የማዕድን ዘርፍን መጠበቅ ለተጠናከረ ብሔራዊ ደህንነት” በሚል ርዕስ የልምድ ልውውጥ አድርጓል፡፡
በልምድ ልውውጡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ÷ ኢትዮጵያ በርካታ ማዕድናት እንዳላት በመግለጽ የመንግስት ፖሊሲና መመሪያ በመሻሻሉ ምክንያትም ለልማት ከፍተኛ አቅም መፍጠሯን ገልፀዋል።
ኢትዮጵያ በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማዕድን አምራች ባለሃብቶች ማራኪ መዳረሻ መሆኗን ጠቅሰዋል፡፡
ሀብቶችን ከሕገ-ወጥ ብዝበዛና ከሕገ-ወጥ ዝውውር መጠበቅ ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ ሚና እንዳለውም አንስተዋል፡፡
ሕገ-ወጥ የማዕድን ሥራ ግጭትን እንዳያባብስ፣ የተደራጁ ወንጀሎችን ተጠናክረው በአካባቢው ማህበረሰብ ሕይወት ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድሩ ፖሊስ ለዘርፉ ትልቅ ትኩረት በመስጠት ኃላፊነት ያለው አስተዳደር ለማረጋገጥ እየሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡
በናይጄሪያ የፌደራል ሪፐብሊክ ጦር ኮሌጅ አዛዥ ሜጀር ጀነራል አይቢ ማይና የተመራው ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የቴክኖሎጂ አቅሞችን ተዘዋውሮ መጎብኘቱን ከፌዴራል ፖሊስ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።