ጁዲት ሱሚንዋ ቱሉካ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሃላ ፈጽመው በይፋ ሥራ ጀምረዋል፡፡
ከቤልጂየም ዩኒቨርሲቲ ሊብሬ ዴ ብሬክስልስ በአፕላይድ ኢኮኖሚክስ የማስተርስ ዲግሪ ያላቸው ቱሉካ፥ ከፈረንጆቹ 2020 እስከ 2023 የፕሬዚዳንት ስትራቴጂክ ክትትል ካውንስል ምክትል አስተባባሪ በመሆን ሲያገለግሉ፤ በ2023 መጋቢት ወር የፕላን ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸው ተገልጿል።
አሁን ደግሞ የሀገሪቱ ምክር ቤት ቱሉካ እና ሌሎች 54 አዳዲስ የመንግስት አስፈጻሚ አባላትን በአብላጫ ድምፅ ካፀደቀ በኋላ በይፋ ስራ መጀመራቸው ተገልጿል።
ቱሉካ በንግግራቸው፥ የመጀመሪያዋ የኮንጎ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ፋና ወጊ በመሆናቸው ኩራት እንደተሰማቸውም ነው የተናገሩት፡፡
ሆኖም የተጣለባቸው ኃላፊነት ቀላል እንዳልሆነ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሯ፥ በኪንሻሳ ወደ 2 ነጥብ 6 ሚሊየን የሚጠጉ የስራ ዕድልና የሂሳብና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የትምህርት ተቋማትን በመገንባት በማደግ ላይ ባለችው ኮንጎ ጥሩ መሰረት ለመጣል ቃል ገብተዋል፡፡
በተጨማሪም በብሔራዊ ደህንነት፣ በኢኮኖሚ ብዝሃነት፣ በመሰረተ ልማት ትስስር፣ በህዝብ አገልግሎቶች እና በአየር ንብረት ለውጥ ላይ እርምጃዎችን አጠናክረን እንቀጥላለን ማለታቸውን የዘገበው ዥኑዋ ነው፡፡
FBC
More Stories
ከባድ የውንብድና እና የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል በእስራት ማስቀጣቱን የሸካ ዞን ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሙስናን ለመከላከል በተደረገው ጥረት ከ85 ሚሊዮን በላይ ብር የህዝብ ሃብት ማዳን ተችላል
ኢትዮጵያ እና ኢንግሊዝ በኢንቨስትመንት፣ በንግድ እና ኢኮኖሚ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ