ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድ እና ልማት ዘርፍ ያላትን ትብብር አጠናክራ እንደምትቀጥል ገለጸች፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከፊንላንድ የውጭ ንግድና ልማት ሚኒስትር ቪሌ ታቪዮ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷በሀገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ተያያዥ ቀጣናዊ ጉዳዮች ዙሪያ በትኩረት መክረዋል፡፡
አምባሳደር ምስጋኑ÷ፊላንድ በኢትዮጵያ በተለይም በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ እንድታደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ፊንላንድ ለኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች ላደረገችው ድጋፍ ምስጋና ማቅረባቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ቪሌ ታቪዮ በበኩላቸው÷ፊንላንድ ከኢትዮጵያ ጋር በንግድና ልማት ዘርፍ ያላትን ትብብር ይበልጥ እንደምታጠናክር ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ ወገኖች በቅርቡ የኢትዮ-ፊላንድ የጋራ የፖለቲካ ምክክር መድረክ ለማካሄድ መስማማታቸውም ተገልጿል፡፡
FBC
More Stories
መንግስት በፈጠራና ክህሎት ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ