ከ371 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ነው 128 ሚሊየን ብር የገቢና 243 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች የተያዙት፡፡
ከተያዙት እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ቡና፣ መድሃኒት፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ የግንባታ እቃዎች፣ አደንዛዥ እፆችና ሌሎች እቃዎች እንደሚገኙበት ተገልጿል፡፡
በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር አዲስ አበባ ኤርፖርት፣ ሞያሌ እና አዋሽ ቅረንጫፍ ጽ/ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።