በአፋር ክልል ዱብቲ ወረዳ የሚገኙ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶችን ወደ ስራ ለማስገባት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢጃራ ተስፋዬ የተንዳሆ እና አላሎ ባድ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶችን ጎብኝተው ፕሮጀክቶቹ ያሉበትን ሁኔታ ተመልክተዋል፡፡የጉብኝቱ ዓላማ ፕሮጀክቶቹ ያሉበትን ችግር ለመፍታትና ወደ ስራ ለማስገባት መሆኑን ከኢንስቲትዩቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡በሚቀጥለው ዓመት ለፕሮጀክቶቹ በጀት በመመድብ ጥገና በማድረግ ወደ ስራ ለማስገባት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነም ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።በተያያዘ በሰመራ ከተማ የሚገኘውን የኢንስቲትዩቱ ንብረቶች ያሉበትን ሁኔታም ተመልክተዋል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።