የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በጎንደርና ባህርዳር ከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የልማትና የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን እየጎበኙ ነው።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) እና የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተር ርስቱ ይርዳው በጎደር ከተማ የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።
በተጨማሪም በክረምቱ ወራቶች በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ሊተከሉ የተዘጋጁ የዛፍና የፍራፍሬ ችግኞችን ዝግጅት በችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ተገኝተው እየተመለከቱ ይገኛሉ።
በከተማው የኢንዱስትሪ መንደሮች ጨምሮ በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በወጭና በተኪ ምርቶች የተሰማሩ ባለሃብቶችን የምርት ሒደት እንደሚጎበኙም ተጠቁሟል።
በተመሳሳይ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተስፋየ ይገዙ በባህር ዳር ከተማ የሚገኙ የተለያዩ መሰረተ ልማት ግንባታዎችን እየጎበኙ ነው።
በከተማው የአረንጓዴ ልማት ሥራዎችና ሌሎች የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችንም እየጎበኙ መሆኑ ተመላክቷል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።