
በሳውዲ አረቢያ የንግድ ምክር ቤት ፌዴሬሽን የተመራ 79 አባላትን የያዘ የሳውዲ አረቢያ የኢንቨስትመንት እና የንግድ የልዑካን ቡድን ኢትዮጵያን ለመጎብኘት ማምሻውን አዲስ አበባ ገብቷል። ጉብኝቱ የሁለቱን ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ትስስር ለማጠናከር ያለመ ሲሆን፤ ልዑኩ በአዲስ አበባ በሚኖረው የሶስት ቀናት ቆይታም ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የማምረቻ ቦታዎችን እንደሚጎበኝ ይጠበቃል።በተጨማሪም የኢትዮ-ሳውዲ አረቢያ የቢዝነስ የምክክር መድረክ እንደሚካሄድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል። በኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤትና በሳውዲ አረቢያ አቻው መካከል የመግባቢያ ስምምነት ይፈረማል ተብሎም ይጠበቃል።
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።