172 ፍልሰተኞች ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸውን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።ኤምባሲውና የዓለም አቀፍ ፍልሰተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) በትብብር በሦስት ዙር 172 መደበኛ ያልሆኑ ፍልሰተኞችን በዚህ ሣምንት በአውሮፕላንና በባቡር ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉ ተገልጿል። የኢትዮ-ጅቡቲ-የመን መንገድ እጅግ አደገኛ ከመሆኑም በላይ በድንበር ተሻጋሪ ሕገ-ወጥ ቡድኖች ምክንያት ዜጎች ለድብደባ፣ እንግልት፣ ዘረፋ እንዲሁም ሞት እየተዳረጉ እንደሚገኙ ኤምባሲው ባወጣው መረጃ አስገንዝቧል።ለዚህም ዜጎች ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ከዚህ መሰል አደጋ ለመጠበቅ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በትብብር በመስራት የጋራ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።