ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት የኢትዮጵያ ስታርትአፕ አዋርድስ መክፈቻ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው።
በመርሐ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚልና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የዓለም አቀፉ ስታርትአፕ አዋርድስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኪም ባልና የተለያዩ ስታርትአፕ ተወካዮች ተገኝተዋል።
መርሐ ግብሩ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከዓለም አቀፉ ስታርትአፕ አዋርድስ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን÷ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርም ተባባሪ አዘጋጅ ነው።
የኢትዮጵያ ስታርትአፕ አዋርድስ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን፤ በመርሐ ግብሩ የተለያዩ ስታርትአፖች ተወዳድረው ለአሸናፊዎቹ ሽልማት እንደሚሰጥ የዘገበው ኢዜአ ነው።
በዛሬው መርሐ ግብር ኢትዮጵያን ወክለው በምስራቅ አፍሪካ የግሎባል ስታርትአፕ አዋርድስ የሚሳተፉ ስታርትአፖች ይፋ ይሆናሉ።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።