የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ በሚገኘው የምክክር ምዕራፍ ሂደት ውስጥ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ተሳታፊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ለመሆኑ እነዚህ የባለድርሻ አካላት ወኪሎች የትኞቹን አካላት ወክለው እየተሳፉ ይገኛሉ?
1. የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች
• ከየወረዳው የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን እንዲወክሉ የተመረጡ ተወካዮች
2. የፓለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች
• በአዲስ አበባ ከተማ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የፓለቲካ ፓርቲዎች
3. የተቋማት እና ማህበራት ተወካዮች (በአዲስ አበባ ከተማ የተመዘገቡ)
• የሃይማኖት ተቋማት
• ሲቪል ማህበራት
• የአሰሪዎች ማህበራት
• የሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን
• የመምህራን ማህበር
• የአካል ጉዳተኞች ማህበራት
• የሙያ ማህበራት
• የቀድማው ሰራዊት ማህበር (ተቀናሽ ሰራዊት ማህበር)
• የጋዜጠኞች ማህበር
• የዩኒቨርሲቲ መምህራን (የመንግስት እና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት)
• የንግድ ማህበራት ምክር ቤት
• የሴቶች እና ወጣቶች ማህበራት
4. የመንግስት ተወካዮች (በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለው ሕግ አውጪ፣ ሕግ አስፈፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ)
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት
• የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት ዳኞች
• የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች
• የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን
5. ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተወካዮች
• በተለያዩ ዘርፎች በህዝብ ዘንድ ቅቡልነት ያላቸው፣ አንቱታን ያተረፉ እና ተፅዕኖን መፍጠር የሚችሉ ግለሰቦች
More Stories
የኢትዮጵያ መንግሥት የ3.5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ ለማድረግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ተፈራረመ
በግብርናው ዘርፍ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ አለባት የሚል ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የ2018 የፌዴራል መንግሥት በጀት 1 ነጥብ 93 ትሪሊየን ብር ሆኖ ጸደቀ