የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ከ14 የምርጫ ክልሎች የሰበሰበውን ውጤት ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚሁ መሰረት ገዢው ፓርቲ ኤኤንሲ 43 በመቶ ድምጽ በማግኘት ሲመራ ዲሞክራቲክ አሊያንስ ፓርቲ ደግሞ በ26 በመቶ ድምጽ ይከተላል።በጁሊየስ ማሌማ የሚመራው ኢኮኖሚክ ፍሪደም ፋይተርስ (ኢኤፍኤፍ) እና በደቡብ አፍሪካ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ የተመሰረተው “ኡምኮንቶ ዊሲዝዌ” ፓርቲ (ኤምኬ ፓርቲ) በተመሳሳይ 8 በመቶ ገደማ ድምጽ ማግኘታቸው ተጠቁሟል።የምርጫው የመጨረሻ ውጤት በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት ይፋ እንደሚደረግ ይጠበቃል። የቅድመ ምርጫ ትንበያዎች የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ፓርቲ ከ30 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በፓርላማ ያለውን አብላጫ መቀመጫ ሊያጣ እንደሚችል ግምታቸውን ያስቀመጡ ሲሆን ይህም ፓርቲው ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ጥምር መንግስት የመመስረት ግዴታ ውስጥ እንዲገባ ሊያደርገው ይችላል ተብሏል።
EBC
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡