በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር” የሚል ቃል አለ፤ ይህን መሰረት ብናደርግ እኛም እርስ በእርሳችን መነጋገራችን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እና አስፈላጊ እንደሆነ የሚያሳየን ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያን ኅብረት ፕሬዚዳንትፓስተር ጻዲቁ አብዶ ገለጹ።የኅብረቱ ፕሬዚዳንት ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ከኢቢሲ ሳይበር ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤በመፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ ጥበበኞች ዘመኑን የሚያውቁ (የሚመክሩ) ‘ይሳኮር’ የሚባሉ ወገኖች እንደነበሩ ተናግረዋል።”ምክር በሰው ልብ እንደጠሊቅ ውኃ ነው፤አዕምሮ ያለው ሰው ግን ይቀዳዋል”ይላል መፅሐፉ የሚሉት ፓስተር ጻዲቁ፤ ሀገራዊ ምክክሩ ሁሉንም የሚያካትት በመሆኑ ያላግባቡን ጉዳዮች ላይ በግልጽ መወያየት አስፈላጊ ነው ይላሉ፡፡”ኢትዮጵያውያን ለብዙ ሺህ ዘመናት በጎውንም ክፉውንም አይተናል ፤ አሁን ላይ ያሉ አለመግባባቶችን ሁሉ ወደ ጠረንጴዛ በማምጣት እና ሀገርን በማስቀደም ልንመክር ይገባል” ብለዋል፡፡
EBC
More Stories
በቀጣይ 90 ቀናት የተቀመጡ ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም እመርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፦አቶ ፍቅሬ አማን
ምክር ቤቶች የህዝቡ ሁለተናዊ ተጠቃሚነት እንድረጋጥ ድርሻቸው የጎላ በመሆኑ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ማጠናከር እንደምያስፈልግ ተጠቆመ ።
ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ እያከናወነች ያለው ተግባር የሚደነቅ ነው