የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያን የልማት እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለፀ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ካደረጉት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሀፊ እና የሰብአዊ እርዳታ አስተባባሪ ዶ/ር ራሚዝ አላክባሮቭ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስትሩ እና ረዳት ዋና ፀሀፊው የመንግስታቱ ድርጅት ለሀገራዊ ልማት ዕቅዶች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያሳድግ በሚያስችሉ ማሻሻያዎች ዙሪያ ተወያይተዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን አጋርነት እና ትብብር የበለጠ በማጠናከር ሀገራዊ የልማት ጥረቶችን መደገፍ እና ለሰብአዊ ሁኔታዎች ምላሽ መስጠት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይም ገንቢ ምክክር ማድረጋቸው ተገልጿል፡፡
እንዲሁም ሀገራዊ የትኩረት መስኮችን እና ትልሞችን እውን ለማድረግ ቅንጅትን እና ውጤታማነትን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም መወያየታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
አምባሳደር ታዬ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ወሳኝ የልማት አጋር እንዲሆን እና ለአባል ሀገራቱ ውጤታማ ድጋፍ ማድረግ እንዲችል የተቋሙን አሰራሮችና ትኩረቶች ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሩ አክለውም ዶ/ር ራሚዝ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግላቸው አረጋግጠውላቸዋል።
ዶ/ር ራሚዝ በበኩላቸው ÷ጽ/ቤታቸው የኢትዮጵያን የልማት እንቅስቃሴዎች ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።