የኢትዮ-ፓኪስታን የኢኮኖሚ ትብብር ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀምሯል፡፡
በፎረሙ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረመስቀል ጫላ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እና ከ80 በላይ የፓኪስታን ባለሃብቶች ተሳትፈዋል፡፡
በተጨማሪም የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሃና አርአያ ስላሴ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ እና ሌሎች የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
ፎረሙ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት፣ የንግድ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ያጠናክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።