በሀገራዊ ምክክሩ የወጣቶችን ሁሉ አቀፍ ተሳትፎ ለማጠናከር የሚያስችል የማህበራዊ ድህረ ገጾች የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ይፋ ተደርጓል፡፡
የወጣቶች ድምጽ ለሀገራዊ ምክክር በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሄደው ንቅናቄ ወጣቶች በሀገራዊ ምክክሩ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ረገድ የመሪነት ሚና እንዲጫወቱ የሚያስችል መሆኑን ተገልጿል።
በንቅናቄው ከተለያዩ ማህበራት የተወጣጡ ወጣቶች፣ በወጣቶች ላይ ትኩረት አድርገው የሚሰሩ በጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ ወጣት የማህበረሰብ አንቂዎች፣ በሚዲያና ፈጠራ ስራ የተሰማሩ ወጣቶችን እንደሚያሳትፍ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ አመልክቷል።
የንቅናቄ መድረኩ ለሶስት ወር የሚዘልቅ ሲሆን ወጣቶችን ተደራሽ ለማድረግ የታለመ መሆኑም ተነግሯል።
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።