
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ያከናወናቸው የዲጂታል ሪፎርም ሥራዎች ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ወንጀልን የመከላከል አቅሙን ከፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን ገለጹ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ዛሬ አመሻሹን የፌደራል ፖሊስ የዜጎች መረጃ መቀበያ ማዕከልን መርቀው ከፍተዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የለማ እና ዜጎች ወንጀልን በቀላሉ ለማዕከሉ የሚጠቁሙበት EFPApp የተሰኘ መተግበሪያንም ስራ አስጀምረዋል።ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በርካታ ሥራዎች መከወናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አውስተው፤ በመንግሥታዊ ተቋማት ከ500 በላይ አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ መደረጋቸውን ጠቅሰዋል።ፌደራል ፖሊስም በማሻሻያው የዲጂታላይዜሽን አሠራርን በመተግበር ህብረተሰቡ በየትኛውም አካባቢ ሆኖ የወንጀል ድርጊትን መጠቆም የሚችልበትን ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ማድረጉ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርለት ተናግረዋል።ሁሉም ዜጋ መተግበሪያውን በመጠቀም ወንጀልን በጋራ የመከላከል ኃላፊነቱን እንዲወጣም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።