በኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የዋጋ ግሽበትን ከነበረበት ወደ በ23 ነጥብ 3 በመቶ ዝቅ ማድረግ መቻሉን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ሚኒስትሯ በሰጡት ማብራሪያ፥ የዋጋ ንረት በተለይም ለምግብ ፍጆታነት የሚውሉ ጥሬ ዕቃዎች በየጊዜው እየጨመሩ በመሆኑ በመንግስት በኩል ቢያንስ እየጨመሩበት ያለውን መጠን ለመቀነስ እየተሞከረ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት መንግስት ነዳጅና ማዳበሪያ ላይ የተለያዩ ድጎማዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡
የኑሮ ውድነት፣ የስራ አጥ ቁጥር መጨመር፣ የውጭ ዕዳዎች አከፋፈል፣ የዓለም የፖለቲካ አቋም መለዋወጥ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ያላቸው ተግዳሮቶች ከፍተኛ በመሆኑ በአንዳንድ ዘርፎች ላይ የታቀደውን ግብ ማሳካት አለመቻሉን ሚኒስትሯ ጠቁመዋል፡፡
የግሉ ዘርፍ ሰፊ የስራ ዕድል እንዲፈጥር በማበረታታት ትልቅ ስራ እየተሰራ ቢሆንም በበለጠ መስራት እንደሚጠበቅ ገልጸው፤ የዘርፎች ተወዳዳሪነትና ምርታማነት አሁንም ትልቅ ስራ የሚፈልግ እንደሆነም አንስተዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ የልማት አጋርነት መቀዛቀዝ በጎረቤትና በሌሎች ሀገራት የልማት ድጋፍ፣ የልማት አጋርነት በተለያዩ በሚያጋጥሙ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት በመቀዛቀዙ፣ የአቅርቦት ሰንሰለት መቆራረጡ ከፍተኛ የሆነ ተግዳሮት በመሆኑ በሀገሪቷ ኢኮኖሚ ላይ ጫና ፈጥሯልም ብለዋል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።