የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከሳዑዲ ዓረቢያ የሰው ሃብትና ማህበራዊ ልማት ሚኒስቴር ዴዔታ አብዲልዋሃብ አልአጌል ጋር በሪያድ ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በዜጎች ሕጋዊ የሥራ ስምሪት ዙሪያ የሁለትዮሽ ምክክር ማድረጋቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ወ/ሮ ሙፈሪያት÷ በሀገራቱ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ማጠናከር በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ትኩረት እንደተሰጠው አንስተዋል፡፡
በሁለቱ ሀገራት የተጀመረው አዲስ የሥራ ስምሪት በአጭር ጊዜ ውስጥ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡንም አብራርተዋል።
ቀጣይ በሁለቱ ሀገራት መካከል ቴክኒካል ቡድን አዋቅሮ በሥራ ሂደቱ ላይ የሚገጥሙ ችግሮችና እድገቶችን እየተወያዩ ለመፍታት ሂደቱን የተሻለ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
አብዲልዋሃብ አልአጌል በበኩላቸው÷ በአዲሱ የሥራ ስምሪት ኢትዮጵያዊያን ተፈላጊነታቸው እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ አሁን የሚታዩ የአሰራር ውስንነቶች በመቅረፍ ለዘርፉ ውጤታማነት በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በሳዑዲ ካላቸዉ ተፈላጊነት አንጻር ሰራተኞችን በማሰልጠን የሥራ ስምሪቱን የተደራጀ ለማድረግ መንግስታቸው እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።