የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከሳዑዲ ዓረቢያ የሰው ሃብትና ማህበራዊ ልማት ሚኒስቴር ዴዔታ አብዲልዋሃብ አልአጌል ጋር በሪያድ ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በዜጎች ሕጋዊ የሥራ ስምሪት ዙሪያ የሁለትዮሽ ምክክር ማድረጋቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡
ወ/ሮ ሙፈሪያት÷ በሀገራቱ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ማጠናከር በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ትኩረት እንደተሰጠው አንስተዋል፡፡
በሁለቱ ሀገራት የተጀመረው አዲስ የሥራ ስምሪት በአጭር ጊዜ ውስጥ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡንም አብራርተዋል።
ቀጣይ በሁለቱ ሀገራት መካከል ቴክኒካል ቡድን አዋቅሮ በሥራ ሂደቱ ላይ የሚገጥሙ ችግሮችና እድገቶችን እየተወያዩ ለመፍታት ሂደቱን የተሻለ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።
አብዲልዋሃብ አልአጌል በበኩላቸው÷ በአዲሱ የሥራ ስምሪት ኢትዮጵያዊያን ተፈላጊነታቸው እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ አሁን የሚታዩ የአሰራር ውስንነቶች በመቅረፍ ለዘርፉ ውጤታማነት በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡
ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በሳዑዲ ካላቸዉ ተፈላጊነት አንጻር ሰራተኞችን በማሰልጠን የሥራ ስምሪቱን የተደራጀ ለማድረግ መንግስታቸው እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።