የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ፎረም “ከፍተኛ ትምህርት ለላቀ ውጤት” በሚል መሪ ሀሳብ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል።ለሁለት ቀናት በሚካሄደው ፎረም ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሸኔ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ለማሻሻል የተለያዩ ተግባራት እየተከናኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል።ሚኒስትር ዴኤታው፤ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል።የጥራት፣ የመልካም አስተዳደር እና የገንዘብ ድጋፍ ችግሮች ተቋማቱን እየፈተ ስለመሆኑ ነው የጠቆሙት።የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ለማሻሻል የሪፎርም ስራዎች እየተተገበረ መሆኑን ገልጸው፤የትምህርት ስርዓቱን ለመቀየር በቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባም አንስተዋል።
EBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።