የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ ለማዘመን ከአዘርባጃኑ ጉብኝት ትልቅ ተሞክሮ ተገኝቷል፡- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
በኢትዮጵያ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ከአዘርባጃኑ ጉብኝት ትልቅ ተሞክሮ መገኘቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትናንትናው እለት በአዘርባጃን ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክቶ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም በአዘርባጃን በተለይ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ በዲጂታል እየተሰጠ እንደሚገኝና ይህም የአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋና ምቹ እንዲሆን ማድረጉን መመልከታቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በተለያዩ ዘርፎች ውጤታማ የሆነ ሪፎርም ማድረጉን ያስታወሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሁን ደግሞ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥን ሪፎርም የማድረግ ስራዎች ተጀምረዋል ብለዋል።
EBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።