የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት፣ የክልል የዘርፉ አስፈፃሚዎችና ባለድርሻ አካላት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም አጠቃቀም፣ በአዳዲስ ኢንቨስትመንት ማስፋት፣ በኢንዱስትሪ ሽግግር፣ በጥናትና ምርምር ዘርፎች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በመድረኩ ገልጸዋል፡፡የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን የዘርፉ ሞተር በማድረግ ዘርፉን ለማነቃቃት በታቀደው መሠረት የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ መናገራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡በዚህም የአምራች ኢንዱስትሪ ዋነኛው ሀገራዊ የርብርብ ማዕከል እንዲሆን ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።