የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት፣ የክልል የዘርፉ አስፈፃሚዎችና ባለድርሻ አካላት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ባለፉት ዘጠኝ ወራት በአምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም አጠቃቀም፣ በአዳዲስ ኢንቨስትመንት ማስፋት፣ በኢንዱስትሪ ሽግግር፣ በጥናትና ምርምር ዘርፎች ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በመድረኩ ገልጸዋል፡፡የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን የዘርፉ ሞተር በማድረግ ዘርፉን ለማነቃቃት በታቀደው መሠረት የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩ መናገራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡በዚህም የአምራች ኢንዱስትሪ ዋነኛው ሀገራዊ የርብርብ ማዕከል እንዲሆን ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
FBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።