በሸገር ከተማ ፉሪ ክፍለ ከተማ መዳ ፉሪ ወረዳ በአንድ መጋዘን ውስጥ በህገወጥ መንገድ የተከማቸ ዘይት፣ ስኳር፣ ዱቄት፣ ሩዝ፣ ምስር እና የአፈር ማዳበሪያ ተያዘ፡፡
የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ፉፋ መገርሳ እንደገለጹት÷ በቀረበ ጥቆማ መሠረት የፍርድ ቤት የፍተሻ ወረቀት በመያዝ በተደረገ ፍተሻ በዛሬው ዕለት ምግብ-ነክ ግብዓቶች እና የአፈር ማዳበሪያው ተይዟል፡፡
በዚህም 1 ሺህ ኩንታል ስኳር፣ 150 ኩንታል ሩዝ፣ 10 ኩንታል ምስር እና 700 ኩንታል የፍርኖ ዱቄት በመጋዘን ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ ተከማችቶ መገኘቱን ነው የገለጹት፡፡
በተጨማሪም 560 ካርቶን ባለ 3 ሊትር እና 4 ሺህ ጄሪካን ባለ 20 ሊትር የምግብ ዘይትን ጨምሮ 250 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መያዙን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።