
የኢትዮጵያና የአሜሪካን 120ኛ ዓመት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የሚያወሳ “120 ዓመታት የሁለትዮሽ ምስላዊ ጉዞ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ምስላዊ ዓውደ ርዕይ በይፋ ተከፍቷል።
በሁነቱ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ፥ ሁለቱ ሀገራት በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ ለ120 ዓመታት የነበራቸውን ትብብር ወደፊትም አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
የሀገራቱን የረጅም ዓመታት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ዓውደ ርዕዩ አጋዥ ምህዳር የሚፈጥር ነው ያሉት ደግሞ የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ናቸው።
ዓውደ ርዕዩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ከሚያዝያ 30 እስከ ግንቦት 18፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከግንቦት 21 እስከ ሰኔ 1 እንዲሁም በሐያት ሪጀንሲ ሆቴል ከሰኔ 10 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ይቆያል ተብሏል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።