
በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ሪያል ማድሪድ ባየር ሙኒክን 2 ለ1 አሸንፏል።
ሪያል ማድሪድ ባየርሙኒክን በድምር ውጤት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለቻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ አልፏል።
ለሪያል ማድሪድ ሁለቱንም ግቦች ባለቀ ደቂቃ ተቀይሮ የገባው ሆሴሉ ሲያስቆጥር፤ ባየር ሙኒክን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ አልፎንሶ ዴቪስ አስቆጥረዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ሪያል ማድሪድ እና ቦርሲያ ዶርትመንድ በዌምብሌይ ስታዲየም የፍፃሜ ጨዋታቸውን ግንቦት 24 ቀን 2016 ዓ.ም ያደርጋሉ።
EBC
More Stories
የሸካ ዞን የታዳጊ ወጣቶች የእግርኳስ ቡድን የ2018 ክልል አቀፍ ውድድር የዋንጫ አሸናፊ ሆነ።
5ተኛው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የባህል ስፖርቶች ውድድር፣ የባህል ፌስቲቫል እና የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር የታለመውን ግብ ያሳካ መሆኑ ተገለጸ።
ባካሪ ሳኛ ኢትዮጵያ ገባ