
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኦሮሞ ሕዝብ ያገኘውን ለውጥ በማስቀጠል ሠላሙን መጠበቅና አንድነቱን ማጽናት እንዳለበት አስገነዘቡ፡፡
ከአራቱም የወለጋ ዞኖች የተውጣጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት ሀገራዊ ለውጡን የሚደግፍ ሰልፍ በነቀምቴ ከተማ ወለጋ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሕዝባዊ የድጋፍ መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ ሠላም፣ አንድነትና የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ላይ ያተኮሩ ሐሳቦችን አንስተዋል::
የኦሮሞ ሕዝብ ያገኘውን ለውጥ በማስቀጠል ሠላሙን መጠበቅና አንድነቱን ማጽናት እንዳለበትም ገልጸዋል፡፡
በአካባቢው የተገኘውን ሠላም ኅብረተሠቡ ማስቀጠል እንደሚኖርበት ማስገንዘባቸውንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።