
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታክቲካል (ስልታዊ) የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልምምድ እንዲደረግ ለሀገሪቱ ጦር ትዕዛዝ መስጠታቸው ተሰምቷል፡፡ልምምዱ አንዳንድ ምዕራባውያን ባለስልጣናት የሚሰነዘሩትን ጠብ አጫሪ መግለጫ እና ዛቻ ተከትሎ የሚካሄድ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ትዕዛዙን ተከትሎ ሩሲያ ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎቿን የማድረግ አቅም በቅርቡ መፈተሽ ትጀምራለች፡፡በልምምዱ የደቡብ ወታደራዊ ዲስትሪክት ሚሳኤል ሃይሎች፣ ወታደራዊ አውሮፕላኖች እና የሩሲያ የባህር ኃይል እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡ልምምዱ ስልታዊ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን አቅም ለመፈተሽ እና በተመረጡ ቦታዎች ለማሰማራት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ፕሬዚዳንት ፑቲን÷ ሩሲያ የግዛት አንደነቷንና ሉዓላዊነቷን ለማስጠበቅ የሀገሪቱ ጦር በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኝ ማረጋገጣቸውንም አር ቲ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።