
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታክቲካል (ስልታዊ) የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልምምድ እንዲደረግ ለሀገሪቱ ጦር ትዕዛዝ መስጠታቸው ተሰምቷል፡፡ልምምዱ አንዳንድ ምዕራባውያን ባለስልጣናት የሚሰነዘሩትን ጠብ አጫሪ መግለጫ እና ዛቻ ተከትሎ የሚካሄድ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ትዕዛዙን ተከትሎ ሩሲያ ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎቿን የማድረግ አቅም በቅርቡ መፈተሽ ትጀምራለች፡፡በልምምዱ የደቡብ ወታደራዊ ዲስትሪክት ሚሳኤል ሃይሎች፣ ወታደራዊ አውሮፕላኖች እና የሩሲያ የባህር ኃይል እንደሚሳተፉ ተገልጿል፡፡ልምምዱ ስልታዊ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን አቅም ለመፈተሽ እና በተመረጡ ቦታዎች ለማሰማራት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ፕሬዚዳንት ፑቲን÷ ሩሲያ የግዛት አንደነቷንና ሉዓላዊነቷን ለማስጠበቅ የሀገሪቱ ጦር በተጠንቀቅ ላይ እንደሚገኝ ማረጋገጣቸውንም አር ቲ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።