

83ኛው የአርበኞች ቀን መታሰቢያ በዓል በአዲስ አበባ አራት ኪሎ የአርበኞች መታሰቢያ ሐውልት በሚገኝበት ስፍራ ተከብሯል፡፡ በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት እና የጥንታዊት ኢትዮጵያ የአርበኞች ማህበር የበላይ ጠባቂ ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ የጥንት አባቶቻችን በአርበኝነት ተጋድሎ ነፃነቷን አስከብረው ያቆዩልንን ሃገር እና ነፃነት አፅንተን ማቆየት የሁላችንም ሃላፊነት ነው ብለዋል፡፡ ትላንት አባቶቻችን ለኢትዮጵያ ነፃነት ህይወታቸውን መስዋዕት ከፍለውልናል ያሉት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፤ አሁን ያለነው ትውልድ ደግሞ የጋራ ጠላታችን የሆነውን ድህነትን በተባበረ ክንዳችን ድል ነስተን የበለፀገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ በትጋት መስራት አለብን ሲሉ ገልፀዋል። በክብረ በዓሉ ላይ የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊትን በመወከል የተገኙት የመከላከያ የሰው ሀብት አመራር ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል ሀጫሉ ሸለመ፤ አርበኝነት በትውልድ ቅብብሎሽ የሚቀጥል የኢትዮጵያዊያን መገለጫ እሴት ነው ብለዋል፡፡
EBC
More Stories
ዜጎች በመልዕክት መላላኪያ አማራጮች በሚፈጸሙ የሳይበር ጥቃቶች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡-የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር
በሸካ ዞን አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የህግ የበላይነትን ለማስከበር ያለመ ዞናዊ የፀጥታ ግብረ ኃይል የምክክር መድረክ በቴፒ ከተማ ተካሄደ
ክልላዊ የተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ ተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በመካሄድ ላይ ይገኛል።