
የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዡዩአን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደመላሽ ገ/ሚካኤል፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች አመራሮችም ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው አሸኛኘት አድርገውላቸዋል፡፡በኢትዮጵያ የነበራቸው የሥራ ጊዜ ስኬታማ እንደነበር የገለጹት አምባሳደር ዣኦ ዡዩአን÷በሁለቱ ሀገራት ያለው ትብብር 50 ዓመታትን ከመሻገሩ ባለፈ ወደ ስትራቴጂያዊ አጋራነት ማደጉን ጠቅሰዋል።አምባሳደሩ በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ያደረጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል፡፡በሥራ ቆይታቸው በቻይና መንግስት ድጋፍ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ የነበሩ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ለፍጻሜ መብቃታቸው ተጠቁሟል፡፡ኢትዮጵያ ብሪክስን እንድትቀላቀል ቻይና ያደረገችው ድጋፍ የሁለቱ ሀገራት የረዥም ዘመን ጠንካራ ወዳጅነት ሌላኛው ማሳያ መሆኑም ተወስቷል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።