
በአሸባሪው ሸኔ ታጣቂዎች ላይ የሚወሰደው የማያዳግም ርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደቡብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሰለሞን ኢተፋ ገለጹ።
የሽብር ቡድኑን በመደምሰስ በአንዳንድ አካባቢዎች የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ከምንጩ ለማድረቅ የሚያስችል ውጤታማ ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
በጥናት ላይ የተመሰረቱ በርካታ ዘመቻዎችን በማድረግ የአሸባሪ ቡድኑን አባላት በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን እና በቡድኑ ታጣቂዎች ላይ የሚወሰደው የማያዳግም ርምጃም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡
በተከናወኑ ሕግ የማስከበር ሥራዎች ሠላም እንዲረጋገጥ ማድረግ ተችሏል ማለታቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።