
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መጪውን የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ለሚኖሩ አቅመ ደካሞችና በዝቅተኛ ኑሮ ለሚገኙ ወገኖች ማዕድ አጋሩ።
ፕሬዚዳንቷ በዚህ ወቅት በስተላለፉት መልዕክት÷ ድጋፉ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ መደጋገፍ የእለት ተእለት ተግባር መሆን እንዳለበት አስገንዝበዋል።
መጪውን የትንሳኤ በዓል ከአቅመ ደካማ ወገኖች ጋር አብሮ ማሳለፍ ይገባል ማለታቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡
የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክፍሉ ገዛኸኝ÷ ፕሬዚዳንቷ ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና አቅርበው መንግስት ለነዋሪዎች ተጠቃሚነት የተለያዩ ድጋፎች እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው ነዋሪዎች ፕሬዚዳንቷ የትንሳኤ በዓልን ተደስተው እንዲውሉ ላደረጉላቸው ድጋፍ አመስግነዋል።
FBC
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የወባ መከላከያ ክትባት በሽታውን ለማጥፋት በማለም ለተጀመረው ርብርብ ትልቅ እገዛ ያደርጋል አሉ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ።