
የሬሚዲያል ፈተና ከሰኔ ወር መጀመሪያ ጀምሮ ይሰጣልየሬሚዲያል ፈተና ከሰኔ ወር መጀመሪያ እስከ 15 ባሉት ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራንና ተማሪዎች ልማት ዴስክ ኃላፊ አቶ በየነ ተዘራ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የዘንድሮውን የሬሚዲያል ፈተና ከሰኔ ወር መጀመሪያ እስከ 15 ባሉት ቀናት በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ለመስጠት እየተሠራ ነው፡፡ባለፈው ዓመት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ ፈተናውን በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ ነው ያሉት አቶ በየነ፤ ፈተናው በኦንላይን፣ በኦንላይንና በወረቀት አልያም በጥብቅ ቁጥጥር በወረቀት ለመስጠት ታቅዶ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡ባለፈው ዓመት ከነበሩ ክፍተቶች ትምህርት በመውሰድ ዘንድሮ ፈተናው በጥብቅ ቁጥጥር በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ መሆኑን በመግለጽ፤ ፈተናው በማዕከል ደረጃ በጥብቅ ቁጥጥር እንደሚከናወን ተመላክቷል።
ምንጭ : ኢ.ፕ.ድ
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።