




የሸካ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት የአስፈጻሚ መምሪያዎች የ2016 በጀት ዓመት የ 9ወራት የተግባር አፈጻጸም ግምገማ መድረክ አጠቃላይ አመራር በተገኙበት በቴፒ ከተማ ማካሄድ ጀመረ።
የ9 ወራት ተግባር ግምገማ መድረኩን የመሩት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ እንደተናገሩት በዚህ አፈጻጸም ላይ ጉለት በታዩት አካባቢ ትኩረት በማድረግ ቶሎ ፈጥኖ በመውጣት የጋራ ርብርብ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
በቀር ሦስት ወራት ውስጥ የ90 ቀናት ዕቅድ በማቀድ ሁሉም የጋራ ቅንጅትና ርብርብ በማድረግ ለስኬታማነቱ ቅንጅታዊ ስራ እንደሚጠይቅ ዋና አስተዳዳሪው በመድረኩ አሳስበዋል።
በመድረኩ ባለፉት 9 ወራት የተከናወኑ ተግባራት በጥልቀት በመገምገም ጉለቶችንና ጥንካሬዎችን በመለየት ለቀር ወራት የጋራ ርብርብ ለማድረግ የስራ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ ይጠበቃል።
በዚሁ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ በኢኮኖሚ ፣በማህበራዊ እና በአስተዳደራዊ ዘርፎች የተከናወኑ ተግባራት ቀርበው በጥልቀት ውይይት እንደሚደረግባቸው ለማወቅ ተችሏል ሲል የዞኑ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ዘግቧል።
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።