ኢራን በደቡባዊ እስራኤል በሚገኝ የኢንዱስትሪ ማዕከል ላይ የሚሳዔል ጥቃት ፈጽማለች፡፡
የእስራኤል ጦር እንዳስታወቀው÷ ቴህራን በኢንዱስትሪ ማዕከሉ ላይ በፈጸመችው የሚሳዔል ጥቃት የኬሚካል ማምረቻ ፋብሪካ በእሳት ተያይዟል፡፡
የእስራኤል ብሄራዊ የእሳት አደጋ መከላከል አገልግሎት በኬሚካል ፋብሪካው ላይ የደረሰውንና በከፍተኛ ሁኔታ የተያያዘውን እሳት ለማጥፋት ርብርብ እያደረገ ይገኛል፡፡
ጥቃቱ በተፈጸመበት አካባቢ የሚገኙ ሠራተኞች አና ነዋሪዎችም ደህንነቱ በተጠበቀ ቦታ እንዲጠለሉ አሳስቧል፡፡
ኢራን አሜሪካና እስራኤል ለሚፈጽሙባት ጥቃት አጸፋ በአካበቢው በሚገኙ የዋሽንግተን አጋር ሀገራት ቁልፍ ተቋማት ላይ ጥቃት እየፈጸመች መሆኗንም ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በተመሳሳይ እስራኤል በኢራን ወታደራዊ የማዘዣ ጣቢያዎች እና የጦር መሳሪያ ማምረቻ ማዕከላት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መፈጸሟ አይዘነጋም፡፡
በሌላ በኩል ኢራን ከሰሞኑ በሳዑዲ ዓረቢያ በፈጸመችው ጥቃት የአሜሪካ ወደታራዊ ጄት ተመትቶ መውደቁ መረጋገጡን ዘገባው አመልክቷል፡፡
More Stories
ሩሲያ ከመጋቢት 23 ጀምሮ የነዳጅ (ቤንዚን) ኤክስፖርት ልታግድ ነው።
ኢራን የፓኪስታን ሰንደቅ ዓላማ የያዙ 20 ተጨማሪ መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ እንዲያልፉ ፈቀደች
የሁቲ ሁለተኛ ዙር ጥቃት እና የአሜሪካ እግረኛ ጦር…