የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን ካልከፈተች በኃይል መሰረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት ለመፈጸም ያስቀመጡትን ቀነ ገደብ በድጋሚ አራዘሙ፡፡
ፕሬዚዳንቱ ከሳምንት በፊት ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን በ48 ሰዓታት ውስጥ ክፍት እንድታደርግ አሳስበው፥ ይህን የማታደርግ ከሆነ በኃይል መሰረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት እንደሚፈጽሙ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል፡፡
ሆኖም ባሳለፍነው ሰኞ ዕለት ከኢራን ጋር ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸው፥ ያስቀመጡትን ቀነ ገደብ ወደ አምስት ቀናት ማራዘማቸው አይዘነጋም፡፡
ኢራን በበኩሏ ከአሜሪካ ጋር የጀመረችው ድርድር እንደሌለ መግለጿ የሚታወስ ሲሆን፥ ፕሬዚዳንቱ ለቴህራን የሰጡትን ቀነ ገደብ ለተጨማሪ 10 ቀናት ማራዘማቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ከሳምንት በፊት ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን በ48 ሰዓታት ውስጥ ክፍት እንድታደርግ አሳስበው፥ ይህን የማታደርግ ከሆነ በኃይል መሰረተ ልማቶቿ ላይ ጥቃት እንደሚፈጽሙ ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል፡፡
ሆኖም ባሳለፍነው ሰኞ ዕለት ከኢራን ጋር ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸው፥ ያስቀመጡትን ቀነ ገደብ ወደ አምስት ቀናት ማራዘማቸው አይዘነጋም፡፡
ኢራን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በላከችው ደብዳቤ፥ ጦርነት አወጁብኝ ካለቻቸው ሀገራትና አጋሮቻቸው ውጪ ያሉ መርከቦች በሆርሙዝ ወሽመጥ እንዲያልፉ መፍቀዷን አስታውቃለች፡፡
More Stories
በ48 ነጥብ 8 ሚሊየን ዶላር ወጪ 500 ሺህ ዘመናዊ ቆጣሪዎችን ለመግጠም እየተሰራ ነው
የእናቶችንና ህፃናትን ሞት ለመቀነስ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኳታር ተወካይ በኢራን ጥቃቶች ዙሪያ ከዚህ በላይ ዝም ማለት አንችልም ሲሉ ተናገሩ።